![](https://arifview.com/wp-content/uploads/2024/06/IMG_20240614_170752_681.jpg)
ዓርብ ሰኔ 07 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በአፋር እና ሶማሊ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የተኩስ አቁም ስምምነቱ ተጥሶ የተጀመረው የትጥቅ ውጊያ እንዲሁም የንጹሀን ጉዳትና መፈናቀል እንዳሳሰበው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ።
ከባለፈው ሳምንት ሐሙስ ግንቦት 30 ቀን 2016 ጀምሮ በአካባቢው ወደ ትጥቅ ውጊያ ያመራ ውጥረት መከሰቱን በተመለከተ መረጃዎች እንደደረሱት ኢሰመኮ ገልጿል።
ኮሚሽኑ ከአፋር እና ሶማሊ ክልል አመራሮች እንዳረጋገጠው በአዋሳኝ አካባቢው “አልፎ አልፎ” ውጊያ ተከስቷል። በውጊያውም ቁጥራቸው በመግለጫው ያልተጠቀሱ ንጹሀን ሰዎች መጎዳታቸው እና መፈናቀላቸው ተጠቁሟል።
የኢሰመኮ ምክትል ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ግጭቱ በአስቸኳይ እንዲቆም የሁለቱ ክልል አስተዳደሮች ዝግጁ በመሆናቸው የፌደራል መንግስቱ ተጨማሪ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል። በተጨማሪም ተፋላሚዎች በኢድ አል አድሃ በዓል መንፈስ ተግባብተው ውጊያው እንዳይባባስ እና ንጹሀን እንዳይጎዱ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
24/7.
Профессиональный сервис сантехников в Сан-Хосе.
Надежные сантехники в Сан-Хосе.
без выходных.
Специальные цены на услуги сантехников в Сан-Хосе.
Экспертные сантехнические услуги в Сан-Хосе.
24 часа в сутки.
Экспертные сантехнические услуги в Сан-Хосе.
Надежные сантехники в вашем районе.
Доступные цены на сантехнические услуги в Сан-Хосе.
plumber in san jose plumbersan-joseca4.com .