![](https://arifview.com/wp-content/uploads/2024/06/photo_2024-06-20_04-38-45.jpg)
የትንሳኤ ሰባ እንደርታ ፓርቲ ዋና ጸሃፊ አቶ ካልአዩ መሐሪ ለጣቢያችን እንደተናገሩት ካለፉት ጥቂት ወራት ወዲህ በክልሉ ህጻናት እና ሴቶችን አግቶ ገንዘብ መጠየቅ እና ጾታዊ ጥቃት ተባብሷል ብለዋል።
የክልሉ መንግሥት ጉዳዩን በሚገባ እያወቀ ለመከላከል ግን ዳተኝነት እንደሚታይበት የሚናገሩት ፀሀፊው፤
በክልሉ ለሚታየው የሴቶች እና ህፃናት መደፈር እና እገታ እንዲሁም ስርዓት አልበኝነት ትጥቅ ያልፈቱ ታጣቂዎች ተባባሪ እንደሆኑም ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ከዚህ ቀደም በትግራይ ክልል የበርካታ አካላት ተሳትፎ ያለበት የተደራጀ የመሬት ወረራ መኖሩን አስታውቆ የነበረው ፓርቲው ገዳዩ ከመቀነስ ይልቅ በከፍተኛ ሁኔታ የመጨመር አዝማሚያ እየታየ እንደሆነም ገልጸዋል።
በለዓለም አሰፋ
ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም