![](https://arifview.com/wp-content/uploads/2024/06/IMG_20240622_113803_862-1024x722-2.jpg)
ሰኔ 15 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ) በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ነው የተባለው የሸገር ታላቁ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በኩራ ጂዳ ክፍለ ከተማ ተካሄደ።
በአምስት ዓመታት እንደሚጠናቀቅ የተመላከተው150 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው መንገድ÷ ሁሉንም የሸገር ከተማ ክፍለ ከተሞች እንደሚያገናኝ ተገልጿል፡፡
በመጀመሪያው ዙር በ4 ነጥን 5 ቢሊየን ብር የ38 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ግንባታ እንደሚከናወን የተገለጸ ሲሆን÷ ይህም ከኩራ ጅዳ በመነሳት ጣፎ፣ ኮዬ ፈጨ እና ገላን ክፍለ ከተሞችን ያገናኛል ተብሏል፡፡